የልደታ አስተዳደር ህንፃ 2ኛ ወለል ቢሮ ቁጥር 205
+251910046729
የቅሬታ አስተያየት መስጫ
ዓርብ, ህዳር 14, 2016 ዓ.ም
መግቢያ
ስለ እኛ
የጽ/ቤቱ ራዕይ ፣ ተልዕኮና እሴቶች
የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት
የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
የዜጎች የስምምነት ሰነድ
አገልግሎቶች
ተቋማዊ አደረጃጀት
ለመልካም አስተዳደር አስተያየት
ለማንኛዉም ቅሬታዎ
ማስታወቂያ
ሚዲያ
ዜና | News
የምስል ክምችት | Photo Gallery
የቪዲዮ ክምችት | Videos
Online TV
መጽሄቶች | Magazines
Web APP
የዛሬይቱ ልደታ | Lideta Today
ጠቃሚ መረጃዎች
ደንብና መመሪያዎች
ብሮሸር
የደንበኞች የእርካታ ዳሰሳ ገጽ
ወረዳዎች
ወረዳ 1
ወረዳ 2
ወረዳ 3
ወረዳ 4
ወረዳ 5
ወረዳ 6
ወረዳ 7
ወረዳ 8
ወረዳ 9
ወረዳ 10
ይግቡ
መግቢያ
ስለ እኛ
የጽ/ቤቱ ራዕይ ፣ ተልዕኮና እሴቶች
የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት
የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
የዜጎች የስምምነት ሰነድ
አገልግሎቶች
ተቋማዊ አደረጃጀት
ሚዲያ
ዜናዎች | News
ፎቶግራፎች | Photo Gallery
ቪዲዮዎች | Videos
Online TV
መጽሄቶች | Magazine
ጠቃሚ መረጃዎች
ደንብና መመሪያዎች
ብሮሸር
የደንበኞች የእርካታ ዳሰሳ ገጽ
Web APP
ወረዳዎች
ወረዳ 1
ወረዳ 2
ወረዳ 3
ወረዳ 4
ወረዳ 5
ወረዳ 6
ወረዳ 7
ወረዳ 8
ወረዳ 9
ወረዳ 10
ያግኙን
ዜና | Oduu | News
ሞዴል ብሎኮችን በመፍጠር ለነዋሪዎች ምቹና ውብ ጽዱ አከባቢ ለማህበራዊ መስተጋብር ያለው ፋይዳ የላቀ መሆኑ ተገለፀ።
ታህሳስ 16, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሞዴል ብሎክ ለመፍጠር እየተሰሩ ያሉ ተግባራትን ገምግሟል። መድረኩን የመሩት የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አሰፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ በክፍለ ከተማችን የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማውን ገፅታ ከመገንባት ባሻገር የንግድ፣ የቱሪዝም መዳረሻ ሆኗል ብለዋል። ሞዴል ብሎክ በመፍጠር ለማህበረሰቡ ጽዱ ውብ ሰላሙ የተረጋገጠ አካባቢን መፍጠር ይገባል ያሉት ወ/ሮ ልዕልቲ ሞዴል ብሎኮችን ለመፍጠር በምንሰራው ተግባር ላይ ባለሞያዎችን ጨምሮ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለበት ብለዋል። የውይይቱ ተሳታፊ ለነዋሪዋሪዎቻችን ሞዴል ብሎክ በመፍጠር ለኑሮ ተስማሚ ሰላሙ የተጠበቀ፣ውብ ና ፅዱ ብሎክ ብሎክ ለመፍጠር ጋር በጋራ መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።
ዜና | Oduu | News
በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እምርታ" የተቀመጡ ግቦች ለማሳካት በስራ እድል ፈጠራና በሌማት ትሩፍት ስራዎችን ትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
ታህሳስ 16, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ የቀጣይ 90 ቀናት በመደመር መንግስት እይታ የተቀመጡ ግቦች በስራ እድል ፈጠራና ሌማት ትሩፋት የንቅናቅ እቅድ ከሚመለከታቸ ባለድርሻዎች አካላት የጋራ አደረገ ። የልደታ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ፍታለው ከፍያለው እንዳሉት የቀጣይ የዘጠና ቀናት እቅድን የስራ እድል ፈጠራና የሌማት ትሩፋት ለማሳካት ሁሉም በራስ መንፈስ ተነሳሽነት ስራዎች በመስራት የሚጠበቅብንን ሀላፊነት መወጣት ይገባዋል ብለዋል የስራ እድል መፍጠር የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚረጋገጥበት በመሆኑ ይህ ተግባር ላይ በፍጥነትና በትኩረት በመስራት ውጤት ማምጣት ይገባል ያሉት አቶ ፍታለው አያይዘው ንቅናቄውን ለማሳካት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ምክትል ስራ አስፈፃሚና ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አራርሳ ድሪባ እንዳሉት የቀጣይ የዘጠና ቀናት እቅድን ለማሳካትና ለተግባራዊነቱ ላይ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት ብለዋል ። በሚፈጠረው የስራ እድል ላይ 75% የወጣቶችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል ያሉት አቶ አራርሳ አያይዘው የሌማት ትሩፋት ላይም የተሰጠውን እቅድ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አሰፋ ቶላ የማይሰሩ እጆች እንዳይኖሩ አዳዲስ ተጠቃሚዎችን በመፍጠር ስራዎችን በልዩ ትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል። ዜሮ ግቦች ላይ ተረጂነትን ለመቀነስ ስራን የሚያማርጥ እጆች እንዳይኖሩ በትኩረት መስራት መቻል አለብን በማለት አቶ አሰፋ ገልፀዋል። ስራዎችን ለማሳካት ስምሪታችንን በማስተካከልና በትኩረት በመምራት ስራዎች በውጤት መታጀብ እንዳለባቸው አንስተዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎችም የስራ እድል ፈጠራና ለሌማት ትሩፍት ተግባራትን በንቅናቄ በመስራት የያዝነውን ግብ በጋራ ማሳካት ይገባናል ብለዋል።
ዜና | Oduu | News
"በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እምርታ' በሚል መርህ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ለማሳካት የሚታየው የአመራሩ ቁርጠኝነትና የህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል" - ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ
ታህሳስ 7, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር "በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እምርታ" በሚል መርህ እየተከናወኑ የሚገኙ የአንድ ወር አፈፃፀም ከአጠቃላይ አመራሩ ጋር በመገምገም በቀጣይ ትኩረት በሚፈልጉ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ አስቀምጧል። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ መድረኩን የመሩ ሲሆኑ በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እምርታ በሚል መርህ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ለማሳካት የሚታየው የአመራሩ ቁርጠኝነትና የህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል። ኢንጂነር ወንድሙ አክለውም ተግባሩ ክፍለ ከተማውን አንድ እርምጃ ከፍ የሚያደርግ በመሆኑ ያለ ምንም መንጠባጠብ በውጤት ለማጠናቀቅ አመራሩ በ24/7 መርህ መስራት እንደሚገባው አፅንኦት ሰጥተዋል። የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ በበኩላቸው በየደረጃው የመደመር መንግሥት የዘርፎች እመርታን ለማሳደግ የተሰጡ ሥልጠናዎችን መነሻ በማድረግ የነዋሪውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ዕቅድ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልፀዋል። በአንድ ወር የታየው አፈፃፀም አበረታች መሆኑን በማንሳት ተግባራቱን ከመደበኛ ዕቅዶች ጋር አጣጥሞ መምራት እንደሚገባ ወ/ሮ ልዕልቲ አሳስበዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍታለው ከፍያለው በመድረኩ እንዳሉት የተያዙት ዕቅዶች ልዩ ርብርብ የሚፈልጉ በመሆናቸው በውጤት ለማጠናቀቅ ሁሉም አካል በቁርጠኝነት ሊረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በመድረኩ በአንድ ወር የተከናወኑ ተግባራት አፈፃፀም የቀረበ ሲሆን የኑሮ ውድነትን ከመቀነስ አኳያ በተለይም የምርት አቅርቦትን ከማሳደግ እና ህገ ወጥነትን ከመከላከል፣ የሌማት ትሩፋት፣ ሌብነትን እና ብልሹ አሰራርን ከመቀነስ፣ ተረጂነትን ከመቀነስ፣ ከሰው ተኮር ተግባራት፣ ከገቢ አሰባሰብ እና ከአገልግሎት አሰጣጥ ስራ አኳያ የተሰሩ ተግባራት አፈፃፀም የተሻለ መሆኑ ተገልጿል።
ዜና | Oduu | News
የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት እየሰራ ያለውን ዘመኑን የዋጀ የኮሙኒኬሽን ስራዎች እና የዲጂታል ሚድያ ተግባራትን ለየካ አቻው ልምዱን አካፈለ።
ታህሳስ 7, 2018
የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት እየሰራ ያለውን ዘመኑን የዋጀ የኮሙኒኬሽን ስራዎች እና የዲጂታል ሚድያ ተግባራትን ለየካ አቻው ልምዱን አካፍሏል። በእለቱም በክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት እየተሰሩ ያሉና ለሌላው ተሞክሮ ይሆናሉ የተባሉ ስራዎችን አስመልክቶ ገለፃ ተደርጓል። የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሲፈን ባዩ ወቅታዊ ስራዎችን ማዕከል ያደረገ የህዝብ ግንኙነት፣ የዲጂታል ሚዲያና የፕሮዳክሽን ቡድኖች በቅንጅት በመስራት የህትመት፣ የዜናና የቪዲዮ ፕሮዳክሽን ስራዎች በሚፈለገው የጥራት ደረጃ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በክከተማው የመረጃ ስርዓትን ዘመናዊ ፣ፈጣንና ተደራሽ ለማድረግ ተጨባጭ ስራ መሰራቱን የጠቆሙት ወ/ሮ ሲፈን የልደታ ፋና ፕሮግራም፣ የቅኝትና የእለታዊ ዜናዎች እንዲሁም የህትመት ስራዎችና ዲጂታል ሚድያ ዙሪያ ሰፊ የማስተዋወቅ ስራ ተሰርቷል ብለዋል። የልምድ ልውውጡ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን በመቅሰም በመንግስትና በህዝብ መካከል የድልድይ ሚናችንን በአግባቡ እንድንወጣ ያግዘናል ያሉት የየካ ክ/ከተማ ኮሚንኬሽን ባለሞያዎች ወደተቀራራቢ አፈፃፀም በመምጣት የጋራ ተልእኮአችንን ለማሳካት በቅንጅት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል ። በመጨረሻም የመረጃ ማዕከልን የጎበኙ ሲሆን የመረጃ አደረጃጀት፣ አያያዝንና የአሰራር ስርዓትን አስመልክቶ የተሰሩ ስራዎችን አይተዋል።
ዜና | Oduu | News
"በአዲስ እይታ የልደታ ከፍታ" የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ለንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የአሰራር ልምዱን አካፈለ
ጥቅምት 16, 2018
የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሲፈን ባዩ በተሞክሮ ልውውጡ ወቅት ባስተላለፍት መልዕክት እንደተናገሩት የኮሙኒኬሽን መዋቅሩ ተቀራራቢ አፈፃፀም እንዲኖረው በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀው የተሞክሮ ልውውጡም ይህንን ለማጠናከር ያስችላል ሲሉ ገልፀዋል። ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ በተሰጠን አቅጣጫ መሰረት እርስ በእርስ መማማርን አዳብረን ጠንካራ የኮሙኒኬሽን ስርዓት እንዘረጋለን ብለዋል ወ/ሮ ሲፈን። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አብዱረዛቅ በበኩላቸው ያገኘነውን ልምድ በክ/ከተማችን በማስፋት ጠንካራ የኮሙኒኬሽን ስርዓት ለመገንባት የሚደረገውን ጉዞ ለማሳለጥ ሚናችንን እንወጣለን ሲሉ ተናግረዋል።
ዜና | Oduu | News
የክፍለ ከተማው አስተዳደር ካቤኔ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሔደ።
ጥቅምት 16, 2018
የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በልማት እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው አጀንዳዎች ዙሪያ ተወያይቶ የውሳኔ ሀሳቦችን አሳርፏል። የካቢኔ አባላቱ በክ/ከተማው እየተሰሩ የሚገኙትን ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን ፕሮጀክቶቹ የደረሱበትን አፈፃፀሞች በመገምገም ውሳኔ ሰጥተውባቸዋል። በክፍለ ከተማው ነዋሪውን በልማት ተጠቃሚ የሚያደርግ፤ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የሚፈቱ ሌሎች መሰረተ ልማቶች እና ፕሮጀክት ግንባታዎች ስታንዳርድ በጠበቀና በተቀናጀ መልኩ መፈፀም እንደሚገባ ተገልጿል። የልማትና የመልካም አስተዳደር እንዲሁም ልዩ ልዩ ፕሮጀክት ግንባታ አጀንዳዎች ላይ ተወያይተን የወሰናቸውን ጉዳዮች በጠንካራ ክትትልና ድጋፍ መፈጸም ከሁሉም አስፈጻሚ አካላት እንደሚጠበቅ ተመላክቷል። የካቢኔ አባላቱ እንደገለፁት የህዝባችንን ተጠቃሚነትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ምላሽ መስጠት የትኩረት ማዕከል አድርገን እየሰራን እንገኛለን ብለው የተቀመጠው የውሳኔ ሃሳብ ተግባራዊ ለማደረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ዜና | Oduu | News
''የኮሙኒኬሽን ስራዎቻችንን በማጠናከር የክፍለ ከተማዋን ገጽታ በመገንባት ልማትን እናፋጥናለን'' ወ/ሮ ሲፈን ባዩ የልደታ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ
ጥቅምት 17, 2018
ኮሙኒኬሽን የመንግስትንና የህብረተሰብን ተሳትፎ አጉልቶ በማውጣትና በማስተባበር በኩል ስኬታማ ስራዎች መሠራት በመቻሉ ጥራቱን የጠበቀ መረጃን በፍጥነት ለማህበረሰቡ ተደራሽ በመደረጉ ሀሰተኛ መረጃን መቀነስ ተችሏል ሲል የልደታ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ገለጸ። የልደታ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የ2018 በጀት የሩብ አመት አፈፃፀም ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ የልደታ ክፍለ ከተማ የኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሲፈን ባዩ በሩብ አመቱ የመንግስትንና የማህበረሰብን ተሳትፎ አጉልቶ በማውጣትና በማስተባበር ስኬታማ ስራዎች መሠራቱን በመግለፅ የማህበረሰብ እና በመንግስት ተሳትፎ የተፈቱ የመልካም አስተዳደር ተግባራትን በተለያዩ የኮሙኒኬሽን አግባቦች በመጠቀም ተደራሽ ማድረግ ተችሏል በማለት ገልፀዋል። የኮሙኒኬሽን ተቋማት የመረጃ አያያዝና አደረጃጀት ይበልጥ በማጠናከርና በማሻሻል ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እንዲኖር ያግዘናል ያሉት ወ/ሮ ሲፈን በሩብ አመት አፈፃፀም ግቦችንና ተግባራትን በተቀመጠው እቅዶች ልክ በወጥነት ማከናወን መቻሉ ገልፀዋል ። የተለያዩ የሀሰተኛ መረጃዎች በማሰራጨት ህብረሰቡ እንዳይረጋጋና ሀገሪቷም ሰላሟንና ጸጥታዋን እንዳታረጋግጥ ተግዳሮት እየሆነ ይገኛል ያሉት ኃላፊዋ ጽ/ቤቱም ከተለያዩ የወረዳና የክ/ከተማ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በሚያደርሰው ትክክለኛ መረጃ የሀሰተኛ መረጃ እንዲቀንስ ማድረግ ተችሏል በቀጣይም የተሻለ መረጃን በጥራት በመስራት ለማህበረሰቡ ተደራሽ እናደርጋለን ብለዋል። የምናስተላልፋቸው መልዕክቶችም የህዝቡን የልማት ተሳትፎ የሚያጎለብቱ እና በመንግስትና በህዝብ መካከል ያለው የልማት ትስስር እንዲጠናከር የሚያደርጉ ሊሆን ይገባል ብለው የመረጃና የኮሙኒኬሽን ስራዎቻችን ለሃገርና ለትውልድ ግንባታ ለማዋል የዘርፉ አመራር፣ባለሙያዎችና ማህበረሰብ አንቂዎች ተግተው መስራት አለባቸው በማለት አክለው ገልፀዋል። በተያያዘም የተቋሙን ስራዎች በተሻለ በማቀናጀት ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ተገቢውን ትኩረት በመስጠት በቅንጅትና በተግባቦት ጥራት ያለው መረጃ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ወ/ሮ ሲፈን ባዩ አንስተዋል። በቀጣይ በጽ/ቤቱ የተከናወኑ ተግባሮች እንዲሻሻሉ የሚደረገው ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ መቀጠል አለበት በማለት በቀጣይ የተሻለ የመረጃ ልውውጥ በማድረግ ቀልጣፍ የሆነ የመረጃ ተደራሽነት እንዲኖር ተግባራትን በቅንጅት መሠራት ይገባል ሲሉ አንስተዋል። ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የ ልደታ ክ/ከተማ ኮሚንኬሽን ገፆችን ይከታተሉ !! http://linktr.ee/lidetacommunication1
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የአዲስ አበባ አስተዳደር ኮሚንኬሽን ቢሮ ባደረገው የ2017 ምዘና ከ11 ዱም ክ/ከተማ 1 ኛ ደረጃን በመያዝ ተሸላሚ ሆኗል።
ነሀሴ 21, 2018
ይህ ውጤት እንዲመዘገብ ስትሰሩ ለነበራቹህ የክ/ከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ፣ ለክ/ከተማ ጽ/ቤቶች፣ ለወረዳ ኮሙኒኬሽን መዋቅር፣ ለምክር ቤት ዘርፍ ኮሚቴ፣ ለማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች፣ለጽ/ቤቱ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ምስጋና እናቀርባለን። ድጋፋቹህ በቀጣይም ተጠናክሮ እንዲቀጥል አደራ እንላለን። ወ/ሮ ሲፈን ባዩ የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ የተገልጋይና ባለድርሻ አካላት ሚና በተመለከተ የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ።
ሀምሌ 10, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ እሸቴ ተገልጋዩ ለመገልገል ሲመጣ የሚጠበቅበትን ነገር በማሟላት የሚፈልገውን አገልግሎት ማግኘት እንደሚችል ገልፀው አገልግሎቱ ቀልጣፋ እንዲሆን ያጎደልነውን ነገር ደግሞ በመወያየትና በመሙላት ቀልጣፍና ውጤታማ እንዲሁም አዳጊ የሆነ አገልግሎት መስጠት ተችሏል በማለት ገልፀዋል። በምንሰጠው አገልግሎት ማህበረሰባችንን ስናገለግል ነበር በማለት በሚሰጡ አገልግሎቶች ተገልጋዩ የሚያነሳቸውን ችግሮች እቅድ በማቀድ በአጭርና በረጅም ጊዜ ለመፍታት የቻልንበት አግባብ አለ ሲሉ ወ/ሮ አበባ እሸቴ ገልፀዋል። ለህብረተሰብ እንቅፍት የሆነ የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ችግር መንግስት ልዩ ትኩረት በመስጠት ስራዎችን መስራት ችሏል። በሚሰጡ አገልግሎቶች የመብራትና የሲስተም መቆራረጥ የሚመለከተው አካል ሀላፊነት ወስዶ እየሰራ መሆኑን የገለፁት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በቀጣይ ያሉትን ችግሮች ቀርፎ ለነዋሪዎቻችን ቀልጣፍ አገልግሎት መስጠት እንዲቻል እየተሰራ ነው ብለዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሓፍቱ ብርሃኑ እንደገለፁት አገልግሎት ፈልጎ ከሚመጣው የማህበረሰብ ክፍል ጋር በመነጋገር ያሉትን ጥንካሬዎች በማስቀጠል ክፍተቶች ደግሞ በቀጣይ ቀርፎ ቀልጣፍ አገልግሎት መስጠት ይገባል ብለዋል። መንግስት ዘመኑን ተገልጋዩን በሚመጥን አግባብ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎቶችን እየሰጠ ነው ያሉት አቶ ሓፍቱ አያይዘው ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎት ለተገልጋዩ ግልፅ በማድረግ ፈጣን አገልግሎት መስጠት ላይ እየመጣ ያለውን ወጤት አጠናክሮ ማስቀጠል የተገልጋዩም የአገልጋዩም ሀላፊነት ነው በማለት ገልፀዋል። በአግባቡ አገልግሎት መስጠት ለህዝብ ዝቅ ብሎ ማገልገል ያስፈልጋል ያሉት አቶ ሓፍቱ ብርሃኑ ከመንግስት ተቋም የሚሰጠው አገልግሎት ለትርፍ ሳይሆን እናንተ በምትከፍሉት ግብር ተቀንሶ የሚከፈለው ስለሆነ ማገልገል ግዴታው ነው ሲሉ ተናግረዋል። አገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ እንዲሆን እየተሰሩ ያሉ ተግባራት ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል በማለት በቀጣይም ፈጣንና ቀልጠፋ አገልግሎ አሰጣጥ እንዲኖር እንደዚ አይነት የህዝብ መድረክ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፍቃድ አገልግሎት 16,000 ሺህ በላይ ወጣቶች በማሳተፍ በገንዘብ ፦እውቀትና ጉልበት ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገለጸ።
ሀምሌ 10, 2018
የልደታ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ምክትል ኃላፊና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሰፋ ቶላ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት በጎ ተግባር በሰውና በፈጣሪ ዘንድም ዋጋ ያለው ነው። በጎ መስራት ለህልውናው የሚሰጠው እርካታ ከፍ ያለ በመሆኑ ወጣቶች ይህንን መልካም ተግባር አጠናክረው መቀጠል አለባቹ ብለዋል። በጎ መስራትን ባህል በማድረግ አቅመ ደካሞችንና አረጋዊያን ለመደገፍ በትብብር መሰራት እንዳለበት የተጠቆመ ሲሆን 18 የትኩረት መስክ የሚሆኑ አጠቃላይ በጎ ተግባራት በልዩ ትኩረት እየተከናወነም እንደሆነ ተናግረዋል። በክ/ከተማው በበጎ ተግባር የሚታወቁ ወጣቶች በክረምት ወራት በጎ ተግባር በንቃት የሚሳተፉበት ወቅት በመሆኑ ልዩ ያደረጋል ብለው የዘንድሮ ክረምት በጎ በንቃት መሳተፍ ያስፈልጋል ብለዋል። በርካታ ወጣቶች የሚሳተፉበት በጎ ተግባር በዋነኝነት የአረንጋዴ አሻራ :ቤት አፍርሶ መገንባት ፥ትራፊክ ፥የክረምት ትምህርት ማስተማር ፥ደም ልገሳ ሲሆኑ አረጋውያንና አቅመ ደካሞችን መርዳትም በመሆኑ ወጣቶች የጀመሩትን በጎ ተግባር እስከሚጠናቀቅ በትኩረት እንዲሰሩ አቶ አሰፋ ቶላ አሳስበዋል። የልደታ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ እጅጋየው አድማሱ በበኩላቸው ወጣቶች በክረምቱ በጎ ፍቃድ ያከናወኑት መልካም ተግባር የህሊና እርካታ የሚሰጥ ከመሆኑ ባሻገር ከመንግስት የሚወጣውን ወጪ ማስቀረት እየቻለ ያለ ስራ ነው ብለዋል። ወ/ሮ እጅጋቸውአያይዘውም በጎ ስራ ዓመቱን በሙሉ የምንሰራው ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ገልፀው ወጣቶች በጉልበታቸውና በጊዜያቸው ሰርተው እያበረከቱ ላለው በጎ ስራም ምስጋና አቅርበዋል። በበጎ ፍቃድ የሰው ህይወት ይቀየራል ያሉት ወ/ሮ እጅጋየው ወጣቱ ለማህበረሰቡ የመስራት ልምድን እያጠነከረ ሀገራዊ አንድነትን የመገንባት ኃላፊነቱን መወጣት አለበት ሲሉ ገልፀዋል። የ2017/18 የክረምት ወራት በጎ ተግባር ከ18ቱ የትኩረት መስኮች እየተከናወነ እንደሆነ ተገልጿል።
ዜና | Oduu | News
'የኮሙኒኬሽን ስራዎቻችንን በማጠናከር የክፍለ ከተማዋን ገጽታ በመገንባት ልማትን እናፋጥናለን'' ወ/ሮ ሲፈን ባዩ- የልደታ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ
ሀምሌ 10, 2018
ኮሙኒኬሽን የመንግስትንና የህብረተሰብን ተሳትፎ አጉልቶ በማውጣትና በማስተባበር በኩል ስኬታማ ስራዎች መሠራት በመቻሉ ጥራቱን የጠበቀ መረጃን በፍጥነት ለማህበረሰቡ ተደራሽ በመደረጉ ሀሰተኛ መረጃን መቀነስ ተችሏል ሲል የልደታ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ገለጸ። የልደታ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የ2017 በጀት አመት አፈፃፀምና የ2018 መነሻ እቅድ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ የልደታ ክፍለ ከተማ የኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሲፈን ባዩ በበጀት አመቱ የመንግስትንና የማህበረሰብን ተሳትፎ አጉልቶ በማውጣትና በማስተባበር ስኬታማ ስራዎች መሠራቱን በመግለፅ የ2017 በጀት አመት የማህበረሰብ እና በመንግስት ተሳትፎ የተፈቱ የመልካም አስተዳደር ተግባራትን በተለያዩ የኮሙኒኬሽን አግባቦች በመጠቀም ተደራሽ ማድረግ ተችሏል በማለት ገልፀዋል። ጽ/ቤቱ እቅዱን መነሻ በማድረግ የተከናወኑ ስራዎች እንዳሉ በማንሳት በዘርፉ ለበርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ስኬታማነት የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል የኮሙኒኬሽን ተቋማት የመረጃ አያያዝና አደረጃጀት ይበልጥ በማጠናከርና በማሻሻል ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እንዲኖር ያግዘናል ያሉት ወ/ሮ ሲፈን በበጀት አመቱ ግቦችንና ተግባራትን በተቀመጠው እቅዶች ልክ በወጥነት ማከናወን መቻሉ ገልፀዋል ። የተለያዩ የሀሰተኛ መረጃዎች በማሰራጨት ህብረሰቡ እንዳይረጋጋና ሀገሪቷም ሰላሟንና ጸጥታዋን እንዳታረጋግጥ ተግዳሮት እየሆነ ይገኛል ያሉት ኃላፊዋ ጽ/ቤቱም ከተለያዩ የወረዳና የክ/ከተማ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በሚያደርሰው ትክክለኛ መረጃ የሀሰተኛ መረጃ እንዲቀንስ ማድረግ ተችሏል በቀጣይም የተሻለ መረጃን በጥራት በመስራት ለማህበረሰቡ ተደራሽ እናደርጋለን ብለዋል። የምናስተላልፋቸው መልዕክቶችም የህዝቡን የልማት ተሳትፎ የሚያጎለብቱ እና በመንግስትና በህዝብ መካከል ያለው የልማት ትስስር እንዲጠናከር የሚያደርጉ ሊሆን ይገባል ብለው የመረጃና የኮሙኒኬሽን ስራዎቻችን ለሃገርና ለትውልድ ግንባታ ለማዋል የዘርፉ አመራር፣ባለሙያዎችና ማህበረሰብ አንቂዎች ተግተው መስራት አለባቸው በማለት አክለው ገልፀዋል። በተያያዘም የተቋሙን ስራዎች በተሻለ በማቀናጀት ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ተገቢውን ትኩረት በመስጠት በቅንጅትና በተግባቦት ጥራት ያለው መረጃ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ወ/ሮ ሲፈን ባዩ አንስተዋል። የምናስተላልፋቸው መልዕክቶችም የህዝቡን የልማት ተሳትፎ የሚያጎለብቱ እና በመንግስትና በህዝብ መካከል ያለው የልማት ትስስር እንዲጠናከር የሚያደርጉ ሊሆን ይገባል ብለው የመረጃና የኮሙኒኬሽን ስራዎቻችን ለሃገርና ለትውልድ ግንባታ ለማዋል የዘርፉ አመራር፣ባለሙያዎችና ማህበረሰብ አንቂዎች ተግተው መስራት አለባቸው በማለት ወ/ሮ ሲፈን አክለው ገልፀዋል። በበጀት አመቱ በጽ/ቤቱ የተከናወኑ ተግባሮች እንዲሻሻሉ የሚደረገው ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ መቀጠል አለበት በማለት በቀጣይ የተሻለ የመረጃ ልውውጥ በማድረግ ቀልጣፍ የሆነ የመረጃ ተደራሽነት እንዲኖር ተግባራትን በቅንጅት መሠራት ይገባል ሲሉ አንስተዋል። ጽ/ቤቱ በ 2017 ዓ.ም ያከናወናቸው የኮሙኒኬሽን ስራዎች የሚበረታቱ ናቸው ብለው እኛ በቅንጅት መስራታችን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የ ልደታ ክ/ከተማ ኮሚንኬሽን ገፆችን ይከታተሉ !! http://linktr.ee/lidetacommunication1
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ Measles and VAS= 23915 Deworming= 18972 ለሚሆኑ ህጻናት ክትባት መስጠት ሊጀመር እንደሆነ የክፍለከተማው ጤና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ግንቦት 19, 2018
ፅህፈት ቤቱ በሰጠን መረጃ ክትባቱ በከተማ ደረጃ ከ600 ሺ በላይ እንደ ክፍለከተማ ደግሞ Measles and VAS= 23915 Deworming= 18972 ህፃናት የተቀናጀ የኩፍኝ መከላከያ ክትባት እንደሚሰጥ ገልፁዋል፡፡ ይህ የክትባት ዘመቻም ከግንቦት 18/2017 ለተከታታይ 10 ቀናት እንደሚሰጥ የፅህፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ አህመድ እንድሪስ ገልፀዋል፡፡ ክትባቱም በመንግስትም በግልም የህፃናት ማቆያ፣ በትምህርት ቤቶች ጊዚያዊ ጣቢያዎች ላይ ይሰጣልም ተብሏል፡፡ በመደበኛ ክትባት ያልጀመሩ፣ ክትባቱን አቋርጠው እቤት ላሉ ህፃናት፣ ለነፍሰጡርና ለሚያጠቡ እናቶች የስርአተ ምግብ ልየታ እንደዚሁም የቫይታሚን ኤ ጠብታና የአንጀት ትላትል መከላከያ ኪኒን የመስጠት፣ የታመሙ ህፃናት በመለየት ወደ ጤና ተቋም መላክ ስራ ከክትባቱ ጎን ለጎን ይሰራለም ብለዋል፡፡ ወላጆችም ይህን በመገንዘብ በተጠቀሰው ቀን ከ9 ወር እስከ 5 አመት የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ህፃናትን ለክትባት እንደዚሁም ጎን ለጎን ለሚሰሩ ስራዎችም ተባባሪ እንዲሆኑ ፅህፈት ቤቱ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
ዜና | Oduu | News
"ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና "!! በልደታ ክ/ከተማ የመጋቢት 24 ፍሬዎች የሆኑ ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ፕሮጀክቶች ተመረቁ
መጋቢት 24, 2018
በክ/ከተማው "ትናንት ፣ዛሬና ነገን ለኢትዮጲያ ልዕልና" በሚል መሪ ቃል እየተዘከረ የሚገኘውን መጋቢት 24 ምክንያት በማድረግ ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል። የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ እሸቴ ባደረጉት ንግግር መጋቢት 24 የሀገራችን ብልፅግና መሰረት የተጣለበት ከድህነት እና ኃላቀርነት ለመውጣት የሚያስችሉ ተግባራት መከናወን የጀመሩበት ነው ብለው በመጋቢት 24 የፕሮጀክቶች አፈፃፀም ከመጓተት ወጥቶ ፕሮጀክቶችን በአጠረ ጊዜ የመፈፀም ባህል የዳበረበት ነውም ሲሉ ገልፀዋል። የለውጡ መንግስት በርካታ የመጋቢት ፍሬዎችን እውን አድርጓል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በተለይም የሀገር ኩራትና ቅርስ የሆነውን የታላቁ ህዳሴ ግንድብ ግንባታ ከቆመበት አንስቶ አሁን ያለበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ በማድረግ እና የትምህርት ቤት ምገባን በማስጀመር ረገድ ውጤታማ ስራ አከናውኗል ሲሉ ተናግረዋል። ፕሮጀክቶች በአጠረ ጊዜ በጥራት እንዲጠናቀቁ 24/7 ሲሰሩ ለነበሩ ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል ዋና ስራ አስፈፃሚዋ። የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ አማካሪ የሆኑት አቶ ጥላሁን ፈቃዱ በበኩላቸው መጋቢት 24 በጠንካራ የስራ ባህል ድህነትን ታሪክ ማድረግ የጀመርንበት እንዲሁም ትውልድን የሚያንፁ ፕሮጀክቶች እውን መሆን የቻሉበት ነው ብለዋል። ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን በጥራትና በፍጥነት መጨረስ ባህል እንዲሆን መሰረት የተጣለበት ነው ያሉት አማካሪው በቀጣይ በርካታ ትውልድ የሚያፈሩ ህንፃዎችን ገንብተን የሀገራችንን ብልፅግና እያረጋገጥን እንቀጥላለን ሲሉ ገልፀዋል። የልደታ ክ/ከተማ የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ናርዶስ መንክር እንደተናገሩት አስተዳደሩ በተቋማት ያሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት በጀት መድቦ ፕሮጀክቶችን እየገነባ ይገኛል ብለው በዛሬው እለትም የመጋቢት ፍሬ የሆኑ ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን በአጠረ ጊዜ በጥራት ገንብተን አጠናቀናል ሲሉ ተናግረዋል። በቀጣይ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች አሉን እነዚህን ፕሮጀክቶች በአጠረ ጊዜ አጠናቀን አገልግሎት እናስጀምራለን ብለዋል አቶ ናርዶስ።
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለ ከተማ "ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና"በሚል ቃል ለነዋሪዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት ተሰጠ
መጋቢት 24, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ከህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን የነፃ ህክምና መርሃ ግብር አካሄደ የልደታ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ደረጄ ድሪብሳ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ከመጋቢት ትሩፋት ውስጥ አንዱ የሆነው የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን በማሻሻልና ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር በትኩረት እየሰራን እንገኛለን በማለት ነፃ የህክምና አገልግሎት በመስጠት ፣በጤና ተቋማት በርካታ ስራዎች በመስራት ጤናማ ዜጋ በመፍጠርና ቀልጣፋ አገልግሎትን በመስጠት ረገድ እየተሰራ ያለውን አጠናክረን መስራት ይገባል ብለዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አህመድ እንድሪስ እንደተናገሩት አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ነፃ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ ጤናቸው የተጠበቀ እንዲሆን ነፃ የህክምና መርሃ ግብር በማዘጋጀት የዜጎቻችንን ጤና የመጠበቅ ተግባር እያከናወንን ነው ከዚህ የተሻለ አገልግሎት የሚያስፈልጋቸው ካሉ ፣ ከሆስፒታሎች ጋር በመተባበር ነፃ የህክምና አገልግሎት እንደሚያገኙ ይደረጋል ሲሉ ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ እንግዳው ጓዴ እንደገለጹልን፤ ለማህበረሰብ የነፃ ህክምና አገልግሎት በመስጠት ጤናማ ህዝብ ለመፍጠር ያለው አበርክቶ የተሻለ መሆኑን የገለፀው በተለይ ህክምናው ብዝዎችን በሽታውን አስቀድመው መከላከል እንዲችሉ ግንዛቤ ከመፍጠር ባለፈ መታከም ለማይችሉ የማህበረሰብ ክፍሎችም ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
ዜና | Oduu | News
ላለፉት ሁለት ቀናት ከሁሉም የኮሪደር ልማት አስተባባሪዎች ጋር በመሆን በ2ኛ ምዕራፍ በከተማችን እየለሙ የሚገኙ ስምንት ኮሪደሮችን የስራ አፈጻጸም ተዘዋውረን ገምግመናል።
መጋቢት 4, 2018
የ2ኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራ 135 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለው የመንገድ ግንባታ፣ 42 ኪ.ሜ የሚረዝም የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራ፣ 431 ሄክታር የሚሸፍን የአረንጏዴ ልማት ስራ፣ በከተማችን ያለውን የትራንስፖርት ስርዓት ለማዘመን ከምንሰራው ስራ በተጨማሪ 23,320 በላይ መኪኖችን የማስቆም አቅም ያለው የፓርኪንግና ተርሚናሎች ግንባታ፣ 112 የህዝብ የመጸዳጃ ቦታዎች ግንባታ፣ 2669 ህንጻዎች እድሳት፣ የህጻናት መጫወቻ ሜዳዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ የህዝብ መዝናኛ ፕላዛዎች፣ የእግረኛ እና የብስክሌት መንገዶችን ያካተተ ሲሆን ከ 62 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ የከተማችን ነዋሪዎች ደግሞ የስራ እድልን የፈጠረ ሰፊ ስራ ነው:: ከተማውን በመበከል የህዝቡን ጤና በመጉዳት ከፍተኛ አሉታዊ ጉዳት ሲያደርሱ የነበሩትን ህግ እና ስርዓት አዉጥተን የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓት በከፍተኛ ደረጃ እየተገበርን ነዉ። የወንዞችን ብክለት በመከላከል በኩል ጽዱ አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ለመፍጠር የብክለት መከላከል ህግ ህብረተሰባችን መቀበሉን እና የየተገበረዉ መሆኑን በጉብኝታችን ወቅት ተመልክተናል:: በተሰጣቸው ጊዜ ገደብ ውስጥ ያልገነቡ እና የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓታቸውን ያላስተካከሉትን በመቅጣት ላይ የምንገኝ ሲሆን ከቅጣቱ በላይ የምንፈልገው ህዝባችን በዋናነት ለራሱ ጤና ሲል የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓቱን እና ብክለት መከላከልን እንዲተገብር በመሆኑ ሁላችንም ለዚህ ርብርብ እንድናደርግ ጥሪ አቀርባለሁ:: ያቀረብንላቸውን ጥሪ በመቀበል ህንጻዎችን በማደስ፣ ቀለም በመቀየር እና በከተማዋ ስታንዳርድ መሰረት መብራት በመዘርጋት እያገዙን የሚገኙ የከተማችን ነዋሪዎች፣ ባለሀብቶች እንዲሁም የመንግስትና የግል ተቋማትን ጨምሮ ሙያዊ እና ቁሳዊ ድጋፍ እያደረጉልን የሚገኙ ነዋሪዎቻችንን በራሴ እና በከተማ አስተዳደራችን ስም ላመሰግናቸው እወዳለሁ:: በቀሪ ጊዜያት ልዩ ክትትል በማድረግ ቶሎ መጠናቅ ያለባቸውን ስራዎች መጨረስ፣ መደገፍ የሚገባቸውን ደግሞ እየደገፍን ህዝባችንን በታማኝነት ለማገልገል በገባነው ቃል መሰረት 2ኛውን ምዕራፍ የኮሪደር ልማት አጠናቅቀን ለግልጋሎት ክፍት የምናደርግ ይሆናል:: ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክ/ከተማ "ንፁህ ወንዞች ፤ለጤናማ ህይወት"በሚል መሪ ቃል የወንዝ ዳርቻ ልማትና ብክለት መከላከል ደንብ ቁጥር 180/2017 ዙሪያ ለአመራሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ
መጋቢት 2, 2018
"የወንዝ ዳርቻዎችን በማልማት እና ከብክለት በመከላከል ውብ ፅዱ እና ለኑሮ ተስማሚ አካባቢን እውን ማድረግ ይኖርብናል" ወ/ሮ አበባ እሸቴ "የከተማችን ወንዞች ተጨማሪ የውበት ነፀብራቅ እንጂ የጤና ጠንቅ ሊሆኑ አይገባም" አቶ ሃፍቱ ብርሀኑ የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር "ንፁህ ወንዞች ፤ለጤናማ ህይወት"በሚል መሪ ቃል የወንዝ ዳርቻ ልማትና ብክለት መከላከል ደንብ ቁጥር 180/2017 ዙሪያ ለአመራሩ የንቅናቄ ማስጀመሪያና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል። የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ እሸቴ በመድረኩ ባስተላለፍት መልዕክት የወንዝ ዳርቻዎችን በማልማት እና ከብክለት በመከላከል ውብ ፅዱና ለኑሮ ተስማሚ አካባቢን መፍጠር ይገባል ብለው የወንዝ ዳርቻዎችን ከብክለት መከላከልና ወንዞችን ማልማት የሁሉም ዜጋና የተቋማት ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። ከተማችንን የበለጠ ውብ ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ የወንዝ ዳርቻ ልማት ወሳኝነት አለው ያሉት ወ/ሮ አበባ ወንዞችን ከብክለት መከላከል እና የወንዝ ዳርጃዎችን ማልማት ትኩረት ተሰጥቶበት እየተከናወነ ያለ ተግባር መሆኑን በማንሳት ማህበረሰቡና ተቋማት ቆሻሻን ወደ ወንዝ ከመልቀቅ ሊታቀቡና መንግስት እያከናወነ ያለውን የወንዝ ዳርቻ ልማት ሊያግዙ ይገባል በማለት ገልፀዋል። የልደታ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃፍቱ ብርሀኑ እንደተናገሩት የወንዝ ዳርቻዎችን በማልማትና ከበካይ ነገሮች በመከላከል ወንዞች የከተማችን ተጨማሪ የውበት ነፀብራቅ እንጂ የጤና ጠንቅ እንዳይሆኑ መስራት ይኖርብናል ብለዋል። መንግስት ከተማችንን ውብ ፅዱና ለነዋሪዎች እንዲሁም ለጎብኝዎች ምቹ ለማድረግ ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ የወንዝ ዳርቻ ልማትና ወንዞችን ከብክለት የመከላከል ተግባር መሆኑን የገለፁት አቶ ሃፍቱ ማህበረሰቡም ሆነ ተቋማት ወንዞችን በመጠበቅ ረገድ የድርሻቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል። የክ/ከተማው የአካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንተነህ በፍቃዱ የወንዝ ዳርቻዎችን የማልማት ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው ማህበረሰቡ ወንዞችን ከባይ ነገሮች በመጠበቅ አገራዊ ግዴታውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል። አቶ አንተነህ አክለውም የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ እና የቁጥጥርና የክትትል ስራን ማጠናከር በትኩረት ይሰራበታል ብለው ግንዛቤ ተፈጥሮላቸው ላልታረሙ ተቋማትና ግለሰቦች በደንቡ መሰረት እንደሚቀጡ ገልፀዋል። ተሳታፊዎች በበኩላቸው የወንዞችን ንፅህና መጠበቅ ጤናማ የሆነ ማህበረሰብ ለመገንባት ያስችላል ብለው የወንዞችን ንፅህና በመጠበቅና በማስጠበቅ ረገድ አመራሩ የድርሻውን ይወጣል ማህበረሰቡም አጋዥ ሊሆን ይገባል በማለት ተናግረዋል። የክ/ከተማው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤትና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ለደንብ ቁጥር 180/2017 ተፈፃሚነት በትጋት እንደሚሰሩም ተገልጿል።
ዜና | Oduu | News
አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን የከፍታችን ማሳያ ነው ሲል የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ገለፀ
የካቲት 25, 2018
በልደታ ክ/ከተማ ነዋሪ የሆኑ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል። የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ እሸቴ እንደተናገሩት አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ኢትዮጲያን ከዓለም ጋር የሚያስተሳስር ነው ብለው ኢትዮጲያን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የማድረጉ ተግባር በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ ይቀጥላልም ሲሉ ገልፀዋል። በኢኮኖሚው ዘርፍ የኢትዮጲያ ከፍታ ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና አለው ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ሁሌም ቢሆን ኢትዮጲያን ከዓለም ጋር ለማቆራኘት ለሚሰሩ የለውጥ መሪዎቻችን ምስጋና ይገባል በማለት ገልፀዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚዋ አክለውም አዲስ አበባን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ ለማድረግ መንግስት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው የሚሰሩ እጆች ሁሌም የለውጥ አብነቶች ስለሆኑ ሁሉም ዜጋ የመሪዎቹን ፈለግ ተከትሎ ሌት ከቀን በመስራት ለውጥ ማስመዝገብ አለበት ብለዋል። የጉብኝቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የለውጡ መንግስት የማይሳኩ የሚመስሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በተግባር አሳክቶ አሳይቶናል ብለው በዛሬው ጉብኝትና በተመለከቱት ስራ መደሰታቸውንም ገልፀዋል። ለዶ/ር ዓብይ አህመድ እና ለከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ምስጋና አቅርበዋል። ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የ ልደታ ክ/ከተማ ኮሚንኬሽን ገፆችን ይከታተሉ !! http://linktr.ee/lidetacommunication1
ዜና | Oduu | News
በብልጽግና ፓርቲ የሴት ክንፍ አባላት በሁለተኛው መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና የቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ውይይት አካሄደ።
የካቲት 28, 2018
ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ሰነድ በልደታ ክፍለ ከተማ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ሀላፊ ቀርቧል የብልጽግና ፓርቲ በሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ባሳለፍቸው ውሳኔዎች ባስቀመጣቸው አቅጣጫዎች የብልፅግና ፓርቲ ሴት ክንፍ አባላትና ደጋፊዎች ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ። የልደታ ክፍለ ከተማ ም/ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ነፃነት ደረሰ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ባስተለፉት መልዕክት በብልጽግና ፓርቲ የጉባኤ ውሳኔው አቅጣጫ ላይ የሴቶች ሚና ምን ይመስላል የሚለው በግልፅ በመወያየት ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል በማለት በሴቶች ተጠቃሚነት ላይ ሰፊ ስራ ሲሰራ የነበረ ሲሆን ይህን ለማስቀጠል በሚቻል መልኩ የሴቷን ውስብስብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል መልኩ ፕሮጀክቶችን በመንደፍ ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ተችሏል በማለት ገልፀዋል። ወ/ሮ ነፃነት አያይዘው ፓርቲያችን ሰው ተኮር ነው ስንል የሰራነው እያንዳንዱ ተግባር ለሴቶች ሁለንተናዊ ብለፅግን በሚያረጋግጥ መልኩ እየተሰራ ሲሆን ከዚህ የበለጠ እንዲሆን በዛሬው ውይይት የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ሁሉም ሚናውን ሊወጣ ይገባል በማለት ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ሀላፊና የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ደረጀ ዲሪብሳ ሴቶች ፓርቲው ያስቀመጠውን አቅጣጫ ተግባራዊ በማድረግ፤ልማትና ሰላምን በማስፈን ረገድ የማይተካ ሚና እንዳላቸው በመግለፅ የብልጽግና ጉዞ ለማፋጠን የሴቶች ሚና ከፍተኛ ነው በማለት ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሰናይት ሞሲሳ በበኩላቸው የብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አባላት በጉባኤው የተቀመጠውን አቅጣጫና ተልዕኮ ተገንዝቦ በብቃት የመፈጸም ሁሉንም ሴቶች ለጋራ አላማ በመሰለፍ ሚናቸውን መወጣት አለባቸው በማለት ገልፀው የሴት ክንፋ ያነገባቸው አላማዎች በኢኮኖሚያዊና በማህበራዊ ብልፅግና ጉዞ ለማሳካት ሚናችሁን ልትወጡ ይገባል በማለት ገልፀዋል። ተሳታፊውም የቀረሰው ሰነድ የተሻለ ነው በማለት የፓርቲውን ውሳኔና አቅጣጫ በመተግበር ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል ሲሉ አንስተዋል። ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የ ልደታ ክ/ከተማ ኮሚንኬሽን ገፆችን ይከታተሉ !! http://linktr.ee/lidetacommunication1
ዜና | Oduu | News
"በሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የመንግስት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ከማስረጽ አንጻር ውጤታማ ስራዎች ተሰርተዋል" የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
የካቲት 28, 2018
በበጀት አመቱ ግማሽ አመት እቅድ በሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የመንግስት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ከማስረጽ አንጻር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ የግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ "ዓላማ ተኮር፤ የተናበበ እና የተቀናጀ የተግባቦት ስርዓት ለእመርታዊ እድገት" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ፥ በግማሽ ዓመቱ ዘርፉ መንግስታዊ አጀንዳዎችን ከማስረጽ አንጻር ውጤታማ ስራዎች ሰርቷል። ዘርፉ ህዝብን በልማት ከማሳተፍ እና ከማነቃቃት አንጻርም አበረታች ስራዎች መከናወኑን ገልጸዋል። በተለይም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር፣እንዲሁም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተሳካ መልኩ እንዲከናወን ዘርፉ በጎ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አንስተዋል። በተጨማሪም እንደ አገር በትኩረት እየተከናወነ በሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ በህዝብ ተሳትፎ እንዲታገዝ ዘርፉ ትልቅ ሚና መጫወቱን ተናግረዋል። በተመሳሳይ እንደ ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን እና የሰንደቅ ዓላማ ቀን የመሳሰሉ አገራዊ ሁነቶች ከተገቢው መልዕክት ጋር መሸፈናቸውን ጠቅሰዋል። እነዚህ ሁነቶችም ለሰላም ግንባታ እና ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በመገንባት ሂደት ትልቅ ውጤት ነበራቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ከዘላቂ ሰላም ግንባታ እንዲሁም አፍራሽ መረጃዎችን ከመከላከል አንጻር አሁንም ብዙ ስራዎች እንደሚቀሩ ማውሳታቸውን ኢዜአ ዘግቧል። በመድረኩ ላይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ሀላፊዎች፣ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሃላፊዎች እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የ ልደታ ክ/ከተማ ኮሚንኬሽን ገፆችን ይከታተሉ !! http://linktr.ee/lidetacommunication1
ዜና | Oduu | News
በዓለም አቀፍ ደረጃ 114ኛ ጊዜ በአገራችን ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ "ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል" በሚል መሪ ቃል የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በማስመልከት የባዛር ፌስቲቫል ተከፈተ።
የካቲት 29, 2018
በልደታ ክፍለ ከተማ የሴቶች ቀንን በማስመልከት በተዘጋጀው የባዛር ፌስቲቫሉ ላይ ሚኒስተሮች ፣ሚኒስተር ደኤታዎች፣ አምባሰደሮች ፣ የከተማ አመራሮች፣ የክፍለ ከተማ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተከፍቷል።
ዜና | Oduu | News
የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ ቤት የመምህራን እና የተማሪዎች ስፖርታዊ ሊግ ውድድር የማጠቃለያ ፕሮግራም አካሄደ።
የካቲት 28, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት የ2017 የትምህርት ቤቶችና "የመምህራን ስፖርት ሊግ ውድድር የትምህርት ቤቶች ስፖርት ሊግ ውድድርን ባህል በማድረግ ጤናማ ንቁና ብቁ ትውልድ እንፈጥራለን" በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ የመዝጊያ ፕሮግራም ተካሄደ የልደታ ክፍለ ከተማ የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሰፋ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች፤ የምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ፣የከተማና የክፍለ ከተማ ባለሙያዎች መምህራን, በተጨማሪም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። ስፖርት ለጤና፣ ለአንድነት፣ ለመቻቻል እና ፍቅርን ለማጎልበት ያለው ሚና የጎላ ሲሆን የነገ ሀገር ተረካቢ በሆኑት ተማሪዎች ውድድር መጀመሩ የሚበረታታ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተገልጿል ስፖርት በአእምሮ የዳበረና በስነ ምግባር የታነፀ ጤናው የተጠበቀ ትውልድ ከማፍራትም ባሻገር የእርስ በእርስ ግንኙነትን ለማጠናከር ይጠቅማል በማለት ገልፀዋል። በክላስተር 1 እና በክላስተር 2 ሲካሄድ የነበረው የመምህራን የእግር ኳስ ውድድር በክላስተር 2 6 ለ1አሸናፊነት ተጠናቋል። በመጨረሻም በውድድሩ ተሳታፊ ለነበሩትና ለአሸናፊዎች የዋንጫ የሰርተፍኬትና የሜዳልያ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለ ከተማ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
የካቲት 29, 2018
"ስነ-ምግባር እና መልካም አስተዳደር ለተሻለ አገልግሎት" በሚል መሪ-ቃል ስልጠና የሰጡት የባለስልጣኑ የስነ-ምግባርና የፀረ ሙስና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ተቋሙ የመልካም አስተዳደር እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የሚያስችል ስልጠና ሰጥተዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት በደንብ ቁጥር 180/2017 የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጠ ስልጠናው ኦፊሰሮች በስነ ምግባር በመታነፅ ነዋሪዎቻችን ላይ ደንብን ተግባራዊ ከማድረጋቸው በፊት ለማህብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር የቅድመ የመከላከል ሥራዎችን መስራት እንዳለባቸው ለማስገንዘብ ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና ነው በማለት የደንብ ኦፊሰር በስነ ምግባር በመታነፅ መልካም አስተዳደርን በመቅረፍ ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባቸው ተገልጿል ። የልደታ ክፍለ ከተማ አካባቢ ጥበቃ በተሰጠው ሀላፊነት አካባቢን በተለይ የወንዝ ዳርቻዎችንን ከብክለት በመጠበቅ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳ እንዲሰጡ ለማድረግ በቅንጅት መስራት ይጠበቅብናል በማለት ገልፀዋል በደንቡ ዙሪያ ግንዛቤ ተፈጥሮ ከአካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመስራትና በትኩረት የተሰጠንን ሃላፊነት መወጣት ይጠበቅብናል ፡፡ በመድረኩ የተላለፍት መልዕክቶችን በመያዝና በመገንዘብ ለሚመለከታቸው አካላት ግንዛቤውን በመፍጠርና በማስጨበጥ የማህበረሰባችን ከደንብ መተላለፍ እንዲቆጠብ ማድረግ ይገባል በማለት ከብክለት ለመከላከል የሚያስችል ግንዛቤ አግኝተናል በማለት ተሳታፊዎች አንስተዋል። በመጨረሻም 2017 በጀት አመት የ6ወር አፈፃፃም የላቀ ውጤት ላስመዘገብ የእውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የ ልደታ ክ/ከተማ ኮሚንኬሽን ገፆችን ይከታተሉ !! http://linktr.ee/lidetacommunication1
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለ ከተማ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ጽ/ቤት የኪነ ጥበብ ምሽት "መግባባትና አብሮነት ለጋራ ህልማችን ስኬት" በሚል መሪ ቃል የልደታ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ገዢ ትርክትን ለማስረፅ ፕሮግራም አካሄደ።
የካቲት 27, 2018
በመርሃግብሩ ላይ የተለያዩ አገራዊ አንድነትን የሚዘክሩ ዘፈኖች፣ ውዝዋዜዎች፣ ስነ ግጥሞችና ሌሎች የኪነ ጥበብ ትዕይንቶች ታይተዋል። በኪነ ጥበብ ምሽቱ ላይ የልደታ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃፍቱ ብርሃኑ፣ የልደታ ክፍለ ከተማ ም/ዋና ሰራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ነፃነት ደረሰ ፣ የክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ም/ሀላፊና የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ደሰጄ ድሪብሳ የክፍለ ከተማ አመራሮችና የወረዳ አመራሮች በትዕይንቱ ላይ ተገኝተዋል። የሀገራችንን ከፍታ በማሳየትና ህብረ ብሔራዊ አንድነት የበለጠ በማጉላት ለጋራ አንድነታችን በጋራ ለመቆም ገዢ ትርክትን ማስረፅ ከሁላችንም ይጠበቃል ። ኪነ -ጥበብ ለሀገር አንድነትና መግባባት እንዲሁም ለጀመርነዉ የብልፅግና ጉዞ ትልቅ መሳሪያና አቅምም ጭምር ነዉ" በአሁን ሰአት እንደ ሀገር ተስፍችን ብሩህ እንዲሆን በልማትና እድገት ጉዞ ላይ እንድናተኩር ከመቼዉም በተሻለ ወቅት ላይ እንገኛለን። በዚህ ጊዜም ኪነጥበብ የሚጫወተዉ ሚና ከፍተኛ ነዉ ። ሀገርን በሁሉም አጀንዳ በአንድነት ለማሰለፍ ኪነጥበብ ትልቅ አርማና መሳሪያ ነው። ሀገር ለዜጎቿ ምቹ ሰላማዊና እድገት ያላት ሆና እንድትቀጥል ብዙ ባለድርሻ አካላት ቢኖሩም እንኳን ኪነጥበብ ያላትን ሚና ግን ማንም ሊመጣዉ አይችልም። ሀገርን በሰዎች ልቦና ዉስጥ በደንብ ቀርጾ አእምሮን፣ እጆችንና እግሮችን በሙሉ አቅም ለሀገር ለማዘጋጀት ኪነጥበብ ያላት ድርሻ ጉልህ ነዉ። " በሀገሪቱ እየታየ ያለውን የሰላም፣ የመቻቻልና የህብረ ብሄራዊነት እሴት በኪነጥበብ ጎልቶ እንዲወጣ ማስቻል አላማ አድርጎ የተዘጋጀ የኪነጥበብ ምሽት እንደሆነም ተገልፃል።
ዜና | Oduu | News
በአለም አቀፍ ለ114ኛ በኢትዮጵያ ለ49ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው የሴቶች ቀን "ፈጣን እና ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል " በሚል የሴቶችና ህፃናት ማ /ጉ/ ፅ/ ቤት ከጤና ጋር በመተባበር የማህፀን በር እና ጡት ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ደም ልገሳ ተደረገ።
የካቲት 27, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ እሸቴ ባስተላለፉት መልዕክት ሴቶችን በሁሉም ዘርፍ ማሳተፍ አስፈላጊነትና ጠቀሜውም እንደ ሀገር የጎላ ነው በማለት በአገር አቀፍና በአለም ደረጃ የሴቶች ተጽእኖ ፈጣሪነት እያየለ መምጣቱን በመግለፅ ይህን ልምድ በማሳደግ ሴቶችን አሁን ካለውም በላይ በሁሉም ዘርፍ ተሳታፊነታቸው ማሳደግ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ የልደታ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ምክትል ሀላፊና የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ደረጄ ድሪባ እንደገለፁት ሴቶች ከወንዶች እኩል ተሳትፎ ማድረግ ይገባታል በማለት ሴት እናቶቻችን እህቶቻችን እንዲሁም ልጆቻችን ላይ የሚደርሰውን ማግለል በማቆም በሁሉም ዘርፍ ሴቶችን በማሳተፍ ውጤታማ መሆን ተችሏል። የልደታ ክፍለ ከተማ ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ጉዳይ ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሄለን መሀመድ እንደገለፁት የሴቶች ጤና በመጠበቅና ሴቶችን በኢኮኖሚ በማብቃት ፣ የሴቶችን በፖለቲካ ተሳትፎ በማሳደግና የሴቶች መብት በማረጋገጥ ረገድ የተሰራ ስራ የተሻለ ነው በማለት በቀጣይም ይህን አጠናክረን ማቀጠል ይጠበቅብናል በማለት ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አህመድ እንድሪስ ባስተላለፉት መልዕክት ማንኛውም ሴት ይህ አስከፊ በሽታ ሲደርስባት ሳይሆን ቅድመ ምርመራ በማድረግ ራሷን በማወቅ ይገባታል በማለት ለሴቶች ትኩረት ሰጥቶ መስራት ለሃገር መስራት መሆኑን ገልፀው የጤና ባለሙያዎች የሚያደርጉትን የስራ ጥረቶች ምስገና አቅርበው።ይህ ምርመራ በነፃ በመምጣቱ ዛሬ የመጣችሁ ሴቶችና ሌሎች ሴቶች ቅድመ ምርመራ በማድረግ ከበሽታው ራሳቸውን እንዲጠብቁ ጥሪ አስተላልፈዋል።
መግቢያ
ስለ_እኛ
የጽ/ቤቱ ራዕይ ፣ ተልዕኮና እሴቶች
የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት
የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
የዜጎች የስምምነት ሰነድ
አገልግሎቶች
ተቋማዊ አደረጃጀት
ሚዲያ
ዜናዎች | News
ፎቶግራፎች | Photo Gallery
ቪዲዮዎች | Videos
መግለጫዎች | Press Release
Online TV
Web APP
መጽሄቶች | Magazine
ጠቃሚ መረጃዎች
ደንብና መመሪያዎች
ብሮሸር
የደንበኞች የእርካታ ዳሰሳ ገጽ
የዛሬይቱ ልደታ
ወረዳዎች
ወረዳ 1
ወረዳ 2
ወረዳ 3
ወረዳ 4
ወረዳ 5
ወረዳ 6
ወረዳ 7
ወረዳ 8
ወረዳ 9
ወረዳ 10
ይግቡ
lidetacommunication@gmail.com
+251910046729