image
image
image
image
image

የቂርቆስ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ከልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ጋር የልምድ ልውውጥ አደረገ።

መስከረም 14, 2018
የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሲፈን ባዩ በልምድ ልውውጡ ወቅት እንደተናገሩት የአሰራር ተሞክሮን መቅሰም ውጤታማ አገልግሎትን ለመስጠት ያስችላል ብለው ቂርቆስ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት በክ/ከተማችን ተገኝቶ ላደረገው የልምድ ልውውጥም ምስጋና አቅርበዋል። የአሰራር ተሞክሮዎችን መለዋወጥ ስራዎችን በእውቀት ለመስራት ያስችላል ያሉት ኃላፊዋ እኛም ከእናንተ እናንተም ከእኛ የቀሰምናቸውን መልካም አሰራሮች በሙሉ አቅም ወደ ስራ በማስገባት የማህበረሰቡን የመረጃ ፍላጎት ማሟላት ይኖርብናል ሲሉ ገልፀዋል። የቂርቆስ ክ/ከተማ አመራርና ባለሙያዎች በበኩላቸው የቀሰምነውን መልካም አሰራር ወደ ተቋማትን ወስደን በማስፋት ውጤታማ ስራ እንሰራለን ብለዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች